SBS Amharic - ኤስ.ቢ.ኤስ አማርኛ - podcast cover

SBS Amharic - ኤስ.ቢ.ኤስ አማርኛ

Independent news and stories from SBS Audio, connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians. - ያልወገኑ ዜናዎችን ያቀርብልዎታል። ከአውስትራሊያ የሕይወት ታሪኮችና አማርኛ ተናጋሪ አውስትራሊያውያን ጋር ያገናኝዎታል።
Last refreshed:
Follow this podcast in the Metacast mobile app to refresh it and see new episodes.
Download Metacast podcast app
Podcasts are better in Metacast mobile app
Don't just listen to podcasts. Learn from them with transcripts, summaries, and chapters for every episode. Skim, search, and bookmark insights. Learn more

Episodes

በአዲስ አበባና ስድስት ክልሎች የተስፋፋው የዝንጀሮ ፈንጣጣ እስካሁን 22 ሰዎችን አጥቅቷል

በወንጀል የተገኘ ንብረትን ሕጋዊ በማስመሰልና ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመርዳት ወንጀሎችን የሚመረምሩ አካላት አስገዳጅ ሆኖ ሲገኝ ከግድያ በስተቀር ያሉ የምርመራ መንገዶችን የሚፈቅደውና አነጋጋሪ የሆነው አዋጅ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀደቀ

Jun 17, 20259 min

SBS 50 ዓመት አስቆጠረ

ከ800 በላይ አውስትራሊያውያን የንጉሥ ልደት የክብር ሽልማት ባሕረ መዝገብ ውስጥ ሠፈሩ

Jun 09, 20255 min

"ኢትዮጵያና ሶማሊያ ታሪካዊ ጠላቶች ናቸው የሚለው በሥፍራው የሌለ ዝማሬ ነው" የቀድሞው የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብዲወሊ መሐመድ አሊ

የቀድሞው የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትርና የፑንትላንድ ፕሬዚደንት ፕሮፌሰር አብዲወሊ መሐመድ ዓሊ፤ በሶማሊያ ውስጣዊ ችግሮች፣ በሶማሊያ የኢትዮጵያ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነትና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ዙሪያ የተካሔደ ውይይት (March 2017)። የSBSን 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል ምክንያት በማድረግ የቀረበ።

Jun 08, 202511 min

የኢድ አል አድሀ በአል እርድ ተድርጎ ድሁች እንዲበሉ የሚደረግበት በአል ነው ።

ሼህ አብዱራህማን ሀጂ ከቢር በአውስትራሊይ የእስልምና እምነት ተከታዮች መሪ ፤ የኢድ አል አድሀ በአል ሀይማኖታዊ ዳራው ፤ ነብዩ ኢብራሂም ልጃቸው እስማኤልን ለመስእዋት ያቀረቡበት እና ፤ የአላህን ቃል መስማታቸውን እና መታዘዛቸውን ያስመሰከሩበት እንደሆነ ይናገራሉ ።

Jun 05, 20259 min

"SBS ለሁሉም ማኅበረሰቦች መድረክ በማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነትና የአውስትራሊያን እውነተኛ ማንነት የሚያንፀባርቅ የሚዲያ ዐውድ እንዲቀረፅ ረድቷል"አምባሳደር አንዋር ሙክታር

አምባሳደር አንዋር ሙክታር መሐመድ በአውስትራሊያ የኢፌዴሪ ኤምባሲ ምክትል የሚሲዮን መሪ፤ የSBSን 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን ያስተላልፋሉ።

Jun 04, 20255 min

"የገጠመን አንዱ ተግዳሮት የሥራ አስፈፃሚው ሕገ ደንቡን መከተል አለመቻል ነው፤ ቦርዱም በቶሎ እርምት ባለመውሰዱ ትንሽ ደከም ብሏል" አቶ ተካ አዲስ

አቶ ተካ አዲስ፤ የቪክቶሪያ ኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ፤ በሥራ አስፈፃሚ አባላት መካከል ተከስቶ ያለውን የአተያይ ልዩነት ማጥበብ እንዳልተቻለና መፍትሔ እንደሚያሻ ይናገራሉ። ግለ ምክረ ሃሳባቸውንም ያጋራሉ።

Jun 04, 202537 min

"እጁን ዘርግቶ እዚህ ላደረሰን የሜልበርንና አካባቢው ሕዝበ ክርስቲያን ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው" መልአከ ፅዮን ቀሲስ እንግዳ ቸሩ ካሣ

የሜልበርን መካነ ሰላም ቅዱስ ልደታ ለማርያም ወገብርኤል ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ፣ የሰበካ ጉባኤ አባላትና ምዕመናን የቤተክርስቲያን ግንባታ ሂደት፣ የምዕመናን ሕብረትና የአስተዋፅዖ ፋይዳዎች አንስተው ይናገራሉ።

Jun 04, 202516 min

"በSBS 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ የአድማጮቻችንና ተሣታፊዎቻችን ትልቅ አሻራ አለ፤ ላመሰግናቸው እወዳለሁ" ጋዜጠኛ ኤልያስ ጉዲሳ

የSBS አማርኛ አገልግሎት ራዲዮ ጋዜጠኛ ኤልያስ ጉዲሳ፤ የSBS 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል ጋር በተያያዘ ከጋዜጠኛነት ሙያ ጅማሮው ተነስቶ የSBS ግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞን ከአማርኛ አገልግሎቱ ጋር አሰናስሎ ማኅበረሰባዊና ሉላዊ አስተዋፅዖዎችን ያነሳል።

Jun 03, 202513 min

"ለSBS እና አድማጮቻችን እንኳን ለ50ኛው ዓመት አደረሳችሁ! አደረሰን! እላለሁ" ጋዜጠኛ ደመቀ ከበደ

ጋዜጠኛ ደመቀ ከበደ በኢትዮጵያ የSBS አማርኛ አገልግሎት ዋና ዘጋቢ ነው። የSBSን 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል አስመልክቶ የግል የሙያ ተሞክሮዎቹን፣ የSBS እና የSBS አማርኛ አስተዋፅዖዎችን ነቅሶ ግለ አተያዩን ያጋራል።

Jun 03, 202513 min

Who are the Stolen Generations? - የተሰረቁት ትውልዶች እነማን ናቸው?

Australia has a dark chapter of history that many are still learning about. Following European settlement, Aboriginal and Torres Strait Islander children were removed from their families and forced into non-Indigenous society. The trauma and abuse they experienced left deep scars, and the pain still echoes through the generations. But communities are creating positive change. Today these people are recognised as survivors of the Stolen Generations. - አውስትራሊያ አሁንም ድረስ አያሌዎች እየተማሩት ያለ የጨለማ ታሪክ ምዕራ...

Jun 01, 202511 min

"እንኳን ለ50ኛው ዓመት አደረሳችሁ! እንደ ማኅበረሰብ፤ መጪው 50ኛ ዓመት ብሩህ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን" ዶ/ር ተስፋዬ ይግዛው

SBS ከ1975 አንስቶ የአውስትራሊያ መድብለባሕል የማዕዘን ደንጊያና ድምፅ ማጉሊያ ሆኖ እስከ 2025 የተጓዘበትን የግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞውን ጁን 9 / ሰኔ 2 ያከብራል። ዶ/ር ተስፋዬ ይግዛው፤ በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ማኅበር ፕሬዚደንት ምልሰታዊ ምልከታቸውን ያጋራሉ።

Jun 01, 202511 min

ስንብት፤ አቶ ብዙአየነህ ኃይለማርያም ይፍጠር 1963 - 2025

የአቶ ብዙአየነህ ኃይለማርያም ይፍጠር ድንገተኛ ሕልፈተ ሕይወት ከቤተሰብ እስከ ማኅበረሰብ አባላት ብርቱ ሐዘንን ፈጥሯል። ሕልፈታቸውንም ተከትሎ አብሮ አደጋቸው አቶ ኬኔዲ ገብረየሱስ "ብዙአየነህ በማኅበረሰቡ ውስጥ ጥሩ ስም ነበረው። ሕልፈቱ በጣም የሚያስደነግጥ፤ በጣም የሚያሳዝን ነው፤ ማኅበረሰቡ ይጎዳል" ሲሉ፤ የረጅም ጊዜ ወዳጃቸው አቶ ልዑል ፍስሃ "ብዙአየነህ ላመነበት ነገር በትጋት የሚሠራ፤ ለዕውቀት ከፍተኛ ቦታ የሚሰጥ፤ ትልቅ ሰው ነበር። ሐዘናችን ጥልቅ ነው" ብለዋል። የአቶ ብዙአየነህ ፀሎተ ፍትሐት ሐሙስ ግንቦት 21 ቀን 2017 / ሜይ 29 ቀን 2025 በሜልበርን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ከጠዋቱ 9:00 am ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው ይፈፀማል።

May 28, 202510 min

Alfred and Clinton are unlikely friends. Their friendship can teach migrant communities about reconciliation - አልፍሬድና ክሊንተን ለወዳጅነት የሚተሳሰቡ ዓይነት አልነበሩም፤ ለወዳጅነት መብቃታቸው ግና የፍልሰተኛ ማኅበረሰባትን ስለ ዕርቅ ግንዛቤ ሊያስጨብጥ ይችላል

Alfred is an Indonesian migrant, and Clinton is an Aboriginal man from Western Australia. Their friendship changed the way Alfred understood his identity as a migrant Australian. - አልፍሬድ የኢንዶኔዥያ ፍልሰተኛ ሲሆን፤ ክሊንተን የምዕራብ አውስትራሊያ ነባር ዜጎች ሰው ነው። ወዳጅነታቸው ከአልፍሬድ አውስትራሊያዊ ፍልሰተኛ ማንነት ግንዛቤ ጋር ተያይዞ ለመለወጥ በቅቷል።

May 27, 20254 min

"ልጄ ገዛኸኝ በመኪና አደጋ ከማለፉ በፊት 'እናቴ ይቅር በይኝ' ብሎኝ ነበር፤ ለካስ ስንብት ነው፤ በሕልፈቱ ልቤ ተሰብሯል" እናት ድንቅነሽ አሸብር

"ጌታሁን በጣም ጥሩ ሰው ነው፤ ተፈጥሮን የሚያደንቅ ነበር። ብንለያይም በሕልፈቱ በጣም አዝኛለሁ" በመኪና አደጋ ሕይወቱ ያለፈ የጌታሁን ዝግታ የቀድሞ ባለቤት ዳናዊት ሕሉፍ። የወጣት ገዛኸኝ ታደሰ ፀሎተ ፍትሐት ቅዳሜ ግንቦት 16 / ሜይ 24 በደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን 9:30 am ከተከናወነ በኋል የቀብር ሥነ ሥርዓቱ የሚፈፀም ሲሆን፤ የአቶ ጌታሁን ዝግታ የቀብር ሥነ ሥርዓት በቅርቡ ይከናወናል።

May 23, 202513 min

ኢትዮጵያ ከቻይና - ቻይና ከኢትዮጵያ የሚሹት ምንድን ነው?

በአሁኑ ወቅት በሕይወት የሌሉት የቀድሞው የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ስዮም መስፍን በሕይወት ሳሉ ከSBS አማርኛ ጋር ባካሔዱት ቃለ ምልልስ የኢትዮ - ቻይና ዲፕሎማሲያዊና ምጣኔ ሃብታዊ ግንኙነቶችንና የወደፊት ውጥኖቻቸውን አጋርተው ነበር (የSBS 50ኛ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ዳግም የቀረበ)።

May 22, 20259 min
For the best experience, listen in Metacast app for iOS or Android