የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ #4 | የትንሣኤ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትንበያና ታሪካዊ ዳራ (ክፍል 1)
በሉቃስ 24፥26-27 ባለው ክፍል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በርሱ ላይ ሊደርስ ስላለው መከራና ሥቃይ፣ እንዲሁም ከዚያ በኋላ ሊሆን ስላለው ክብር ተግባራዊነትና አስፈላጊነት በሙሴ፣ በነቢያትና በመጻሕፍት ሁሉ አስቀድሞ ስለመነገሩ ከትንሣኤው በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ተናግሮ ነበር።
This is the Amharic version of the Great Truths Podcast.
ይህ ፖድካስት የእግዚአብሔር ቃልን በተሻለ መንገድ ለመረዳት እና የመፅሐፍ ቅዱስን መልዕክት ዛሬ ለእኛ ምን እንደሆነ ለማወቅ ይረዳናል። ታላቅ እውነት (Great Truths) ለትርፍ ያልተቋቋመ፣ ከ 10 ሚሊዮን በላይ የሆኑ የወንጌል አማኝ መሪዎችን (መጋቢዎች፣ እረኞች፣ ቄሶች፣ ሰባኪዎች፣ እና ወንጌላውያኖችን) ለማገልገል የሚፈልግ፣ ደግሞም በአለማችን ያሉ 660 ሚሊዮን ወንጌል አማኝ ክርስትያኖችን ከፍተኛ ጥራት ባላቸው የሚዲያ አማራጮች መፅሐፍ ቅዱስን ለማስተማር የሚሻ ተቋም ነው። ለበለጠ መረጃ እና የእያንዳንዱን ምዕራፍ ሙሉ መፅሐፍ ከተጨማሪ ግብዐቶች ጋር ለማግኘት ድህረ ገፃችንን ይመልከቱ https://amharic.greattruthsglobal.org/